Check out changes at Finote Selam

Check out the new Finote Selam after being A capital city of W/Gojjam zone early this year.

Finote Selam new Music

new music by solomon demle .

public library in Finote Selam

time to support our people.

Finote Selam

time to support our people.

Thanks for Visiting

Sunday, September 23, 2012

Teddy Afro New Wedding Song - Yemushiraye Enat


Tuesday, September 4, 2012

ዚተማርንበትም ዚተማሚርንበትም ሰሞን



(ፎቶው ዚቢቢሲ ነው)
ዹጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት ኚተሚዳበት ሰዓት ጀምሮ ሀገራቜን አዲስ መልክ ይዛለቜ፡፡ ያለፉት ቀናት ስለራሳቜን ዚተማርንባ቞ው፤ በራሳቜንም ዚተማሚርንባ቞ው ቀናት ነበሩ፡፡ እስኪ ኚተማርንባ቞ው ልጀምር፡፡
ትዝ ይለኛል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ኹውጭ ሀገር ወደ አዲስ አበባ ዚሚገቡበት ጊዜ ነበር፡፡ በቩሌ ጎዳና ፖሊሶቜ አዚህም እዚያም በዛ ብለዋል፡፡ እኔ ደግሞ አልሰማሁም ነበርና እዚያ አካባቢ ለሥራ መሄድ፡፡ ኚጥቂት ደቂቃዎቜ በኋላ መንገዱ ጭር አለ፡፡ ፖሊሶቜም መጡና ኚአካባቢው ዘወር እንድንል ነገሩን፡፡ ዹሚገርመው ነገር ግን አካባቢው በአፓርታማዎቜ ዹተጠቀጠቀ ነበርና ዘወር ዚምንልበት ቊታ ጠፋን፡፡ ፖሊሱ ግን አሁንም አሁንም ኚአካባቢው ዘወር እንል ዘንድ ያዝዛል፡፡ ግን ዚት ዘወር እንበል? በመጚሚሻ መጣና በአፓርታማው ዚታቜኛው ክፍል ካሉት ቀቶቜ አንዱን አንኳኳ፡፡ አንዲት በእድሜ ጠና ያሉ ሎት ኚፈቱ፡፡ ‹‹áŒá‰¡›› አለን ፖሊሱ፡፡ አንድ ሰባት እንሆናለን፡፡ ግራ ገብቶን ተያዚን፡፡ ኚጀርባቜን ገፋ ገፋ እያደሚገ ሰው ቀት ውስጥ አስገባን፡፡ ስለ ቻይና ባቡርና ፖሊስ ያዚሁት ፊልም ነው ትዝ ያለኝ፡፡ ሎትዮዋ በሩን እንዲዘጉ ተነገራ቞ው፡፡ ተዘጋ፡፡
አሁንም ሰው ቀት ገብተን ተያዚን፡፡ ደግነቱ ሎትዮዋ ተግባቢ ናቾውና ‹‹á‰ áˆ‰ እንግዲህ መንግሥት ካዛመደን ዐሹፍ በሉና ሻሂ ጠጡ›› አሉን፡፡ እኛም ሳቅ እያልን ባገኘነው ወንበር ተቀመጥን፡፡ እዚያ ተቀምጠንም በባለ ሥልጣኖቻቜንና በሕዝባ቞ው መካኚል ስላለው ግንኙነት ተቾን፤ አማን፤ ሃሳብም ሰነዘርን፡፡ ኹዚህ በፊት ያጋጠመንንም ተጚዋወትን፡፡
ዹጠቅላይ ሚኒስትሩ አስኚሬን በመጣበት ማታ ይህንን አጋጣሚ ነበር ዚማስበው፡፡ ሕዝቡ ግልብጥ ብሎ መንገድ ላይ ወጥቶ ነበር፡፡ በአንዳንድ አደሚጃጀቶቜ በኩል ኚመጡ ጥቂት ሰዎቜ በቀር አብዛኛው ሰው በራሱ ፈቃድ ኀዘኑን ለመግለጥ ታሪክም ለማዚት ነበር ዚወጣው፡፡ ጧፍ እንኳን ያበራው ዕለቱ ዚፍልሰታ ጟም ማብቂያ ዚኪዳነ ምሕሚት ዋዜማ በመሆኑ በቩሌ መድኃኔዓለም፤ በኡራኀል፣ በእስጢፋኖስና በግቢ ገብርኀል አካባቢ ለበዓሉ ጧፍ ለመሞጥ ኚተቀመጡት እናቶቜ እዚገዛ ነበር፡፡ ጧፍ ማብራትን ሕዝቡ ራሱ ያመጣው ዚአቀባበል ሥርዓት ነበር፡፡ ኚዚያ በኋላ ግን በዹ ቀበሌው ተዳሚሰ፡፡
ያን ምሜት ሕዝቡ ወደ ቩሌ አውሮፕላን ማሚፊያ በሰላምና ያለ አንዳቜ ቜግር ሲገባ ነበር፡፡ ኚፖሊስ ጋር ግርግር ዹፈጠሹ አልነበሹም፡፡ ጚዋነት ጎልታ ዚወጣቜበት ምሜት ነበር፡፡ በመንገድም ላይ ቢሆን ዹነበሹው ሁኔታ አስቀድሞ ያልተገመተው ዚሕዝቡ ማዕበል ኹተጠበቀው በላይ መሆኑ ነበር፡፡ ዚጞጥታ አስኚባሪዎቜ መጀመርያ ላይ አስኚሬኑ ኚሕዝብ ርቆ ግራና ቀኝም ተኹልሎ እንዲያልፍ አስበው ነበር፡፡ ሕዝቡ ግን ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ እያለቀሰና እዚተኚዘ አብሮ መጓዝን መሹጠ፡፡ ነገሩንም ሲሚዱት እነርሱም ተውት፡፡ እንዲያ ዝናብ እዚቀጠቀጠው፤ እንዲያ ብርድ እያንቀጠቀጠው ዚዐሥር ደቂቃ መንገድ አራት ሰዓት እስኪፈጅ ድሚስ አስኚሬኑን በክብር አጅቩ፤ ራሱ ባወጣው ሥርዓትና አሠራር ተጓዘ፡፡ ምንም ዓይነት ዚጞጥታ ቜግር ሳይፈጠር አስኚሬኑ ቀተ መንግሥት ደሹሰ፡፡
ለመሆኑ ኹዚህ መማር ዚለብንም?
ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ጹዋ ሕዝብ ነው ስንል ምን ማለታቜን ነው?
ይህ ሕዝብ መሪዎቜ ወይም ባለ ሥልጣናት ባለፉ ባገደሙ ቁጥር ሊንገላታ ዚማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ሊኹበር እንጂ ሊሰጋ ዚማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ቀርበው ሊያወያዩት፤ ቜግሩን በቅርብ ሊያዩለት ዚሚገባ ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ወደ ሀገሪቱ ኚሚመጡ እንግዶቜ በላይ ሊኹበር ዚሚገባው ሕዝብ ነው ማለታቜን ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ቩሌ አውሮፕላን ማሚፊያ ተገኝቶ ዘመዱን ለመቀበል አትገባም ውጭ ቆመህ ዝናብ ይቀጥቅጥህ ሊባል ዚማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ፍትሕ ለማግኘት ዓመት ሁለት ዓመት ሊጉላላ ዚማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ በጎ ለሚሠሩ ሁሉ ስሕተታ቞ውንና ጥፋታ቞ውን እያወቀ እንኳን ዹሚደግፍ ነውና ሊያሳዝኑትና ሊያቀስቀይሙት ዚማይገባ ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ኮንደሚንዚም ብርቅ ሊሆንበት ዚመይገባ ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ለመጀመርያ ጊዜ በሕዝብ ታጅበው ቀተ መንግሥት ሲገቡ አዹሁ፡፡ ምናለ በሕይወት በነበሩ ጊዜ ይህ ሆኖ በነበሹ፡፡ ይኌው ሕዝብ ነውኮ ያኔም ዹነበሹው፤ ይኌው ጹዋ ሕዝብ እኮ ነው ዚሚያጅባ቞ው፤ ይኌው ጹዋ ሕዝብ እኮ ነው ዹሚጠይቃቾው፤ ዚሚያወያያ቞ው፡፡ ይህ ሕዝብኮ እዚሁ ዹነበሹ ነው፡፡ ኚአውሮፓ ወይም ኚእስያ አልመጣም፡፡ ቀጣዮቹም ባለሥልጣናት ይህንን ትምህርት መውሰድ አለባ቞ው፡፡ ባለ ሥልጣናት ሆይ ሰው ሁኑ፡፡ ሰው ያልሆነው አምላክ እንኳን ሰው ሆኖ በሰው ቋንቋ ተነጋግሯል፡፡ ኹሰው ጋር ውሎ አድሯል፤ ኹሰው ጋር በልቷል፡፡ ኹሰው ጋር ተጉዟል፡፡ እናንተ ታድያ ሰው ብትሆኑና ኹሰው ጋር ብትኖሩ ምናለበት? እርሱ አምላካቜን ሰው ሆኖ ዹሰውን መኚራ፣ ስቃይና ኀዘን ቀምሶታል፡፡ እናንተስ ሰው ሆናቜሁ መኚራቜንን፣ ቜግራቜንንና ኀዘናቜንን ብትቀምሱት ምናለ? እስኚ መቌ በሪፖርትና በስብሰባ ብቻ እንገናኛለን? እስኚ መቌ በ቎ሌቭዥን ብቻ እንተያያለን?
ሪፖርት ቢጜፉት እንደ አካል አይሆንም
቎ሌቭዥን ቢያዩት እንደ አካል አይሆንም
ስብሰባ ቢጠሩት እንደ አካል አይሆንም
እንገናኝና ልናገር ሁሉንም
ተብሎ መዘፈኑን አልሰማቜሁም?
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ቀተ መንግሥት ተኹፈተ፡፡ ይህ ደግሞ አቶ መለስ ዚሠሩት ሌላው ታሪክ ነው፡፡ እኔ ስለዚህ ቀተ መንግሥት ክፉ እንጂ ደግ ሰምቌ አላውቅም ነበር፡፡ በተለይ በደርግ ዘመን ስለነበሚው ሁኔታ ዚተጻፉት ሁሉ ስለዚያ ቀተ መንግሥት ዹሆሹር ፊልም ያህል ሲያስፈራሩን ነበር፡፡ ምናልባት ሕዝብ በብዛት ሆኖ ወደዚያ ቀተ መንግሥት ዚገባው በንጉሡ ጊዜ ግብር ለመብላት ሳይሆን አይቀርም፡፡ እርሱንም ሰምተን እንጂ አላዹንም፡፡ ኚዚያ ወዲያ ባለፉት ዓርባ ዓመታት ለሕዝብ ዹተኹለኹለ ቊታ ነበር፡፡ እንዎው አልፎ አልፎ ኚተለያዩ አካላት ጋር ውይይት ካልኖሚ በቀር ቀተ መንግሥቱና ሕዝቡ በማኅበራዊ ነገር አልተገናኝተውም ነበር፡፡
(ፎቶው ዚቢቢሲ ነው)
እነሆ ሕዝብ ተሰለፈና ቀተ መንግሥት ገባ፡፡ ይህንንም ቢሆን ሕዝብ ዹፈጠሹው ይመስለኛል፡፡ ዚአቶ መለስ ሞት ኚተሚዳበት ሰዓት ጀምሮ ሚዲያዎቹን ያጚናነቀው ጥያቄ ዚት ሄደን ልቅሶ እንድሚስ? ዹሚለው ነበር፡፡ ዚቀብር አስፈጻሚው ብሔራዊ ኮሚ቎ም ለዚህ በጎ ምላሜ በመስጠቱ ይመሰገናል፡፡ ወደ ቀተ መንግሥት እንደሚገባ በቀበሌም በአደሚጃጀትም፣ በሚዲያም ኚመነገሩ በፊት ነበር ሕዝብ ቀተ መንግሥቱን ያጥለቀለቀው፡፡ [እዚህም ላይ ሌላ አስመራሪ ነገር ገጥሞን ነበር፡፡ በሀገር ውስጥ ያሉት ዚመንግሥት ሚዲያዎቜ ሰው ግልብጥ ብሎ ዚወጣው ዹጠቅላይ ሚኒስትሩን ፖሊሲና ስትራ቎ጂ ሙሉ በሙሉ በመቀበሉና በመጠቀሙ ነው ይሉ ነበር፡፡ ዚውጮቹ ደግሞ ተገድዶና ተደልሎ ነው፤ አደርባይ ስለሆነም ነው ይላሉ፡፡ ዚሁለቱም ቜግር ሕዝብን ካለ ማወቅና ለራሱ ጥቅም ሁሉንም ነገር ኚመጎተት ዚመጣ ነው፡፡
አስኚሬኑ አዲስ አበባ ሲገባም ሆነ በቀተ መንግሥቱና በዚአካባቢው በተኹናወነው ልቅሶ ሕዝቡ በፖሊሲዎቜና በስትራ቎ጂዎቜ ሙሉ በሙሉ ተስማምቶ ብቻ ዚወጣ አይደለም፡፡ ምክንያቱ ልዩ ልዩ ነው፡፡ በርዕዮተ ዓለማቾውና በሥራ቞ው ተደስቶ ነገር ግን በሆነው ነገር አዝኖ ዚወጣ አለ፡፡ በአንዳንድ ሃሳባ቞ው ተስማምቶ በሌላው ተለያይቶ በመሞታ቞ው ግን አዝኖ ዚወጣ አለ፡፡ በእርሳ቞ው አስተሳሰብም ሆነ ሥራ ምንም ሳይስማማ፣ ነገር ግን ዚሀገሩ መሪ በመሞታ቞ው አዝኖ ዚወጣም አለ፡፡ ታሪክ ለማዚት ሲልም ዚወጣም አለ፡፡ እርሳ቞ውን እዚተቃወመም በባሕሉ ልቅሶ መድሚስ አለብኝ ብሎ ዚወጣም አለ፡፡ ይህ ሁሉ እኛን ይደግፋል ብሎ ማሰብና በዚህ ተመሥርቶ ውሳኔ መወሰን ኚስሕተት ይጥላል፡፡
ይህ ሕዝብ ተገድዶ ዚወጣ አድር ባይ ነው ብሎ ማሰብም ሌላው ስሕተት ነው፡፡ ምናልባት እንዲያውም አብዛኛው ኀዘኑን በባህሉ መሠሚት ለመግለጥ ዚወጣ ነው፡፡ ጥቂት ሊገደዱ ዚሚቜሉ ይኖራሉ፤ ታይተዋልም፡፡ ውጡ ብለው መመርያ ለማውጣት ዚሞኚሩ ታናናሜ ባለ ሥልጣናትም ነበሩ፡፡ ሕዝቡ ግን ዹተጓዘው በራሱ ነው፡፡ መቌም ሕዝብን በግድ ማሰለፍና አደባባይ ማውጣት ይቻል ይሆናል እንጂ እንዲያለቅስ፣ እንዲደነግጥ፣ ፌንት እንዲያደርግ፤ መሬት እንዲንኚባለል ማድሚግ ዚሚቻል አይመስለኝም፡፡ በርግጥ ለደሚት ድቂያ፣ ለአስለቀሜና ለእድር ድንኳን አንዳንድ ቅመማ ቅመም ሳይጚመርበት አይቀርም፡፡ ሁሉንም በአንድ ፋይል ጠቅልሎ ተታልሎ ነው፣ ተገድዶ ነው፣ አድር ባይ ሆኖ ነው ማለት ግን ዚኢትዮጵያን ሕዝብ አለመሚዳትን ዚሚያሳብቅና ወደ ተሳሳተ ውሳኔም ዚሚያደርስ ነው፡፡]
ሕዝቡ ባህላዊ ሕዝብ ነው፡፡ አዛኝ ሕዝብም ነው፡፡ ያዘነበት ዚዚራሱ ምክንያት አለው፡፡ አንድ ያደሚገው ማዘኑ ነው፡፡ ራሳ቞ውን ዚሚስቱ፤ ዚሚያደርጉትን ዚማያውቁ፤ እዚሆነ ያለውን ነገር መቀበል ያቃታ቞ው፤ ዚነገሮቜ መገጣ ጠም ያስደነገጣ቞ው፤ መሪ ሲሞት፤ ሲለቀስለትም አይተው ባለማወቃ቞ው ግራ ዚገባ቞ው ሰዎቜ ነበሩ፡፡ ሁሉም ግን አዝነው ነበር፡፡ ሕፃናት፣ ወጣቶቜ፣ ዐዋቂዎቜ፣ አሚጋውያን፤ ዚተማሩ፣ ዹኹተማ ዹገጠር ሁሉም ወደ አራት ሰዓታት ዹፈጀ ሰልፍ ይዘው ኀዘናቾውን ለመግለጥ ገብተዋል፡፡[እዚህ ላይ ግን ሌላ ዚሚያስመርር ነገር ነበር፡፡ ሕዝብ አዝኗል፡፡ ኀዘኑን ዚሚገልጥበት ቊታም ይፈልጋል፡፡ በባሕላቜን ኀዘናቜንን ዚምንገልጥበት ቊታ እንፈልጋለን፤ እገሌ ሞተ ሲባል ልቅሶ ዹሚደሹሰው ዚት ነው? መባሉ ዹተለመደ ነው፡፡ አንዳንድ እወደድ ባዮቜ ግን ልቅሶውንና ወደ ቀተ መንግሥት መሄዱን እንደ ግዎታ ለማድሚግ ሞክሹዋል፡፡ ለምን? ይህ ኹማማሹር በቀር ምን ፋይዳ ይሰጣል? ወይስ እኛ ያልሠራነው ሥራ እንደ ተሠራ አይቆጠርም? በመጚሚሻዎቹ ሊስት ቀናት በተደሹገው ዚስንብት መርሐ ግብር ጊዜ በዚአካባቢው ዚታዚው አስገዳጅ ዹመሰለ ቅስቀሳ ዚሕዝቡን ስሜት ወደ መሚበሜ ተሻግሮ ነበር፡፡ ፈጜሞ መደገም ዚሌለበት አስመራሪ አሠራር አንዱ ይኌ ነው፡፡]
ምንም እንኳን ዚሕዝቡ ቁጥር ኹተጠበቀው በላይ ቢሆንም፤ ምንም ያህል ያልታሰበ ቢሆን ሕዝቡን ለማስተናገድና ሕዝቡም እንዳይ቞ገር ለማድሚግ ዚጞጥታ አስኚባሪዎቜ ያደርጉት ዹነበሹው ጥሚት ሊደነቅ ይገባዋል፡፡ ዹማመናጹቅ፤ ዚመሳደብ፤ ዹመገፍተር፣ አይቻልም አይቻልም ብሎ ዚመዝጋት ጠባይ አይታይም ነበር፡፡ መጀመርያ በአንድ በር ፤ በኋላም በሁለት በር፤ ኚዚያም በዋናው በር በኩል በማስገባት በመስተንግዶ ሠልጥነዋል ኚሚባሉት ኹሆቮል አስተናጋጆቜ እንኳን በማይገኝ ትኅትናና ቅልጥፍና ለማስተናገድ ጥሚዋል፡፡
እኔ ይህንንም ነገር ነው እንማርበትና እንቀጥል ዹምለው፡፡ ድሮ ድሮ ሌባና ፖሊስ ስንጫወት ፖሊስ አባራሪ ሌባ ተባራሪ ይሆን ነበር፡፡ ይህ ጚዋታ ሌባ በሌለበትም ሳይቀጥል አልቀሹም፡፡ ሕዝብና ፖሊስ ተኚባብሮ እንጂ ተፈራርቶ መኖር ዚለበትም፡፡ ፖሊስ ሕዝቡን ዚሚያገለግል፤ ለሕዝቡም ጞጥታ ዹሚተጋ መሆኑን ማስመስኚር አለበት፡፡ ፖሊስን ወንጀለኛ ብቻ እንዲፈራው መደሹግ አለበት፡፡ ‹‹á–ሊስ እጠራብሃለሁ›› እያሉ ልጆቜን ማስፈራራት እንዲቀር ፖሊሶቹ ራሳ቞ው መሥራት አለባ቞ው፡፡
ይህ ዹአሁኑ ትውልድ ቀተ መንግሥት ምን እንደሚመስል፤ ዚሚመራው ሰው ዚት እንደሚሠራ፤ ዚት እንደሚኖር ለመጀመርያ ጊዜ ያዚበት ዕድል ነው ዹገጠመው፡፡ እንዲያውም አንዳንዶቜ ዹጠቅላይ ሚኒስትሩን ቢሮና ቀት አይተው ተገርመዋል፡፡ እንደዚያ እንደማይመስላ቞ው ይናገሩ ነበር፡፡ ካሰቡት በታቜ ሆኖባ቞ው ‹‹áŠ¥áŠ’ህ ሰው እዚህ ነበር እንዎ ዚሚኖሩት?›› ብለዋል፡፡ ለምን ግን ዚራሳቜንን ቀተ መንግሥት በሕልም ብቻ እንድናዚው ተደሹገ? ለምንድን ነው ስለ መሪዎቻቜን ብዙ ነገር እንዳናውቅ ዹሚደሹገው? ብናውቅ ምን ይሆናል? ያኔስ ቢሆን አሁን ያወቅነውን አልነበር ዹምናውቀው? ምን ዹተለዹ ነገር ነበሹው?
ስለ አቶ መለስ ጠባያት፣ ዚሥራ ሁኔታ፤ ትጋትና ማንነት በሕይወታ቞ው እያሉ ኹምናውቀው በላይ አሁን ነው ዹሰማነው፡፡ መስማታቜን እሰዚው፡፡ ግን ይህንን ቀደም ብሎ መስማት አይቻልም ነበር? በርግጥ እርሳ቞ው ስለ ራሳ቞ው መናገርም ሲነገር መስማትም ብዙም አይፈልጉም ነበር ይባላል፡፡ ዚርሳ቞ው አለመፈለግ መልካም፡፡ ግንኮ መሪ ዹሚፈልገውን ብቻ አይሠራም፤ ሕዝብ ዚሚያስፈልገውንም ጭምር እንጂ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ማለት ግለሰብነት ብቻ አይደለም፡፡ ሕዝባዊ አካልም ነው፡፡ ሕዝብ ስለ መሪው ማወቅ አለበት፡፡ ሊነገሹው ይገባል፡፡ ስለ መሪው ዚማያውቅ ሕዝብ ሁለት ነገር ይገጥመዋል፡፡ ወይ ባለ ማወቅ መሪውን ይቃወመዋል፤ ወይም ባለ ማወቅ መሪውን ይደግፈዋል፡፡ ሁለቱም ግን አደገኞቜ ናቾው፡፡ ባለማወቅ ዹደገፈም ሲያውቅ ይሞሻል፤ ባለማወቅ ዹተቃወመም ሲያወቅ ይፀፀታል፡፡
ኹሁሉም በላይ ዚተደነቅኩት ግን በቀብሩ ዕለት ነው፡፡ በሕይወቮ ይሆናል ብዬ ኚማላስባ቞ው ነገሮቜ አንዱ ዹሆነውም ትናንት ነው፡፡ አንድ ወዳጄ ማታ ስደውልለት ‹‹á‰ áŒ á‰…ላይ ሚኒስትሩ ቀት ጾሎተ ፍትሐት ልናደርግ መሄዳቜን ነው›› አለኝ፤ አላመንኩትም፡፡ ሰዓቱ ኚምሜቱ ወደ ሊስት ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡ ካህናቱ፣ ዲያቆናቱ፣ መሪጌቶቹ ተሟልተው ሙሉ ጞሎት ሲደሚግ ነበር ያደሚው፡፡ ዚቀተ መንግሥቱ ሰዎቜ ለጞሎቱ ዚነበራ቞ው ክብርና ሥነ ሥርዓት ዹሚገርም ነበር፡፡
ኚዚያም ዚኢትዮጵያ ቎ሌቭዥን ዚመጚሚሻውን ዚጞሎት ሥነ ሥርዓት አሳዚን [ግን ጋዜጠኞቹ ምን ነክቷ቞ው ነው? ሃይማኖታዊ ጞሎት ሲሉ ዚዋሉት፡፡ ለመሆኑ ሃይማኖታዊ ያልሆነ ጞሎት አለ? ‹áá‰µáˆá‰µ› ዹሚለው ቃል ጠፍቷ቞ው ነው? ዚቻይናው ቎ሌቭዥን እንኳን ያወቀውን ቃል እነርሱ ምነው ጠፋቾው? ይባስ ብለው በቅድስት ሥላሎ ካ቎ድራል ዹነበሹውን ጞሎት ‹á‰…ዳሎ› እያሉ ይጠሩት ነበር፡፡ ለነገሩማ ‹á‰ á‰…ድስት ሥላሎ ካ቎ድራል› ለማለት ‹á‰ á‰…ድስት ካ቎ድራል ሥላሎ› ይሉ እንደነበር ስሰማ ይቅር ብያ቞ዋለሁ፡፡ ኧሹ እንዲያውም ዚዛሬው ልቅሶ ዚሚያምር ልቅሶ ነው ያለን ጋዜጠኛም ነበር፡፡
 áˆšá‹²á‹«á‹Žá‰»á‰œáŠ• ኚልምድ ማነስም ሊሆን ይቜላ ዚቜግርንና ዹኀዘንን ወቅት እንዎት መዘገብ እንደሚቻል መማር አለባ቞ው፡፡ ሁለት ሳምንት ሙሉ ዹፍቅር እስኚ መቃብርን ዋሜንት ብቻ ኚማሰማት ዚተለያዩ ፕሮግራሞቜን ማዘጋጀት አይቻልም ነበር? ስለ አቶ መለስ ማንነት ዚሚያውቋ቞ውን ማነጋገር፤ ዚውይይት መርሐ ግብር ማዘጋጀት፤ ሌላም ሌላም አይቻልም ነበር? ዹቃለ መጠይቅ ጥያቅዎቹስ ለሕፃኑም፣ ለዐዋቂውም፣ ለተማሹውም፣ ለማይሙም አንድዓይነት መሆን አለባ቞ው? ራሳ቞ው ጋዜጠኛ ራሳ቞ው ተንታኝ እንዲሆኑስ ዚቱ አሠራር ነው ዹፈቀደው? አንዳንዎ እንዲያውም  ስብኚትም ሁሉ ይመስል ነበር? ደግሞስ ሰው አኳሜቶና አጋንኖ ዹሚናገሹውን ነገር ሁሉ ማቅሚብ አለባቜሁ? ጋዜጠኞቻቜንኮ ስለ አቶ መለስ ሁሉን ዐዋቂ ሆኑብን፤ ቢያንስ አብሚዋ቞ው ዚተጓዙት፤ አብሚዋ቞ው ዚሠሩት፤ አብሚዋ቞ው ዚኖሩት፤ ስለ እርሳ቞ው ዚጻፉት ቀርበው ቢነግሩን ምናለ? ይቺ አሠራር ታስመርራለቜና መታሚም አለባት]፡፡
ወደ መስቀል አደባባይ ዹተጓዘውም ኚፊትና ኹኋላ ድባብ በያዙ ካህናት፣ ማዕጠንት በያዙም ጳጳሳት ታጅቊ ነበር፡፡ ይቅርታ ይደሹግልኝና ካለፈው ጊዜ ይልቅ ዚፓትርያርኩ ቀብር ዹመሰለን ይኌኛው ነው፡፡ ዹጉዞው ሥነ ሥርዓት አዘጋጆቹንም ሆነ አኚናዋኞቹን ያስመሰገነ ነበር፡፡ እመለስበታለሁ፡፡
በመስቀል አደባባይ መርሐ ግብሩ በጞሎት መጀመሩን ሳይ ዓይኔ ነው ወይስ ቎ሌቭዥኑ ነው? አሰኝቶኛል፡፡ ይህ እንዲሆን ያደሚገ ማነው? ዚአቶ መለስ ኑዛዜ? ዚወይዘሮ አዜብ ፍላጎት? ወይስ ዚመንግሥት ፈቃድ? ኚወሬ ባለፈ መሹጃ ባውቀው እንዎት በወደድኩ፡፡ መቌም ሰው ሆኖ ኚሥላሎ ቀት ዹሚቀር ዹለምና ዚአቶ መለስ አስኚሬን ወደ ቅድስት ሥላሎ ቀተ ክርስቲያን ሲገባ ዹነበሹውን ሥነ ሥርዓት ምነው ኚሳምንት በፊት ልናዹው አልቻልንም አሰኝቶኛል፡፡
አስኚሬኑ በቀተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠሚት ቀተ መቅደሱን ዞሮ ነው ወደ መቃብሩ ዚገባው፡፡ ባለፈው ጊዜ ይህንን አላዚሁምሳ? ዚካህናቱ ወሚብ፣ ዚሰንበት ተማሪዎቹ መዝሙር፣ ዚአቡነ ናትናኀልና ዚአቡነ አሹጋዊ ትምህርት ‹‹áŠ¥á‹áŠá‰µ ለአቶ መለስ ነው ይህ ዹሚደሹገው?›› አስብሎኛል፡፡ መለስ ኚሕይወታ቞ው ይልቅ[በሕይወታ቞ው ዚሠሩትን እንዲህ በሚታይና በሚሰማ ደሹጃ ስለማላውቅ] በሞታ቞ው ቀተ ክርስቲያንን ኹፍ ኹፍ አድርገዋታል፡፡
ይህቺ ቀተ ክርስቲያን ምን ያህል ክብርና ሞገስ እንደምትሆን ተተኪዎቜም ትምህርት ይወስዳሉ ብዬ አስባለሁ፡፡
መሪ በመፈንቅለ መንግሥት ሳይገለበጥ፤ በጊርነት ተሾንፎ አገር ጥሎ ሳይወጣ፤ በአብዮት ኹዙፋን ወርዶ እሥር ቀት ሳይገባ በተፈጥሮ ሞቶ በክብር ሲቀበር ለእኔ ትውልድ አዲስ ታሪክ ነው፡፡ ዹኔ ትውልድ ስለ መሪው ስደትና ሞት ሲሰማ እንጂ መሪውን አልቅሶ ሲቀብር አላዹሁም፡፡ መለስ በዚህ ታሪክ ሠርተዋል፡፡
ኚቀተ መንግሥት እስኚ መስቀል አደባባይ፤ ኚመስቀል አደባባይ እስኚ ቅድስት ሥላሎ ካ቎ድራል ዹነበሹው ሥነ ሥርዓት አዘጋጆቹንም፣ ተሳታፊዎቹንም ዚሚያስመሰግን ነበር፡፡ ዚፕሮግራሙ በተያዘለት ሰዓት ማለቅ፡፡ በተለይም አቶ ኩማ ደመቅሳ እንኳንም መድሚኩን ለ‹‹áŠ áˆ­á‰²áˆµá‰¶á‰œ›› አልሰጡብን ብያ቞ዋለሁ፡፡ እንዲህ እጥር ምጥን አድርገው አይመሩልንም ነበር፡፡ [በዚሁ ግን አንድ አስመራሪ ነገር መናገር ያስፈልጋል፡፡ ሰሞኑን ይወጡ ዚነበሩ ግጥሞቜ ኚታገል ሰይፉ ግጥም በቀር ሚዛን ዹሚደፋ አጣሁ፡፡ ትትትትትት፣ንንንንንን፣ ቜቜቜቜቜቜ፣ ምምምምምም ብቻ ዚተደሚደሚባ቞ው ናቾው፡፡ አንባቢዎቜም ለመድሚኩ ዚማይመጥኑ፣ ግጥሙንም ወደ ስድ ንባብ በመቀዹር ዚተካኑ ናቾው፡፡ ኚተዘፈኑትም መካኚል ኚአንዱ በቀር ዚግጥም ለዛ ያለው ዹለም፡፡ ምነው ለቾበር ቻቻ እንጂ ለኀዘን ዹሚሆን ግጥም አጣንሳ]
ያ እንደ ደዶፍ ዹወሹደው ዝናብ ሥነ ሥርዓቱን ሳያሰናክለው፡፡ ኚፖሊሶቹና ኚወታደሮቹ ቆብ ላይ ዝናቡ እንደ ጣራ ፍሳሜ እዚወሚደ ሥነ ሥርዓቱ ግን ቀጠለ፡፡ መንገዱ ሁሉ ጎርፍ ነበሹ፡፡ ተጓዊቹ ግን ቜግሩ ሳይፈታ቞ው እነርሱም ጚዋነታ቞ውን አሳይተዋል፡፡ በቀተ ክርስቲያኑ ዹነበሹው ሥነ ሥርዓትም በተያዘው ሰዓት ዹተኹናወነና ለዓይን ዚማይጎሚብጥ ነበር፡፡ አቶ መለስ ተነሥተው ዹሰሞኑን ሁኔታ ቢያዩ በአንዳንዱ ነገር ዹሚገሹሙና ዹሚደነቁ፤ በአንዳንዱ ነገር ዚሚያዝኑና ዚሚቆጩ፣ በአንዳንዱም ነገራቜን ዚሚናደዱ ይመስለኛል፡፡
በዚያም ተባለ በዚህ ግን አቶ መለስ በሞታ቞ው ታሪክ ሠሩ፤ እኛም በሳ቞ው ሞት ታሪክ አዹን፡፡ 
Source Daniel Kibret's view 

Tuesday, August 21, 2012

Ethiopia - Information Minister, Bereket Simon Press conference on the death of Meles Zenawi


አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ Haile Mariam Desalegne named acting Prime Minister




ዹጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሕልፈተ ሕይወት አስመልክቶ መግለጫ ዹሰጠው ዚመንግሥት ኮሙኒኬሜን ጉዳዮቜ ጜሕፈት ቀት፣ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በሙሉ ሥልጣን አገሪቱን እንደሚመሩ አስታወቀ፡፡

በሚኒስትር ማዕሹግ ዚጜሕፈት ቀቱ ኃላፊ አቶ በሚኚት ስምኊን በሒልተን ሆቮል ዛሬ ማለዳ በሰጡት መግለጫ፣ አቶ ኃይለ ማርያም በተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትርነት አገሪቱን ይመራሉ ብለው፣ በሚቀጥለው መስኚሚም መጚሚሻ ዹሚሰበሰበው ፓርላማ ዚሚቀጥለውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡፡ ዹጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ዚቀብር ሥነ ሥርዓት ዚሚያስፈጜም ሰባት አባላት ያሉት ብሔራዊ ምክር ቀት መቋቋሙንም አቶ በሚኚት አስሚድተዋል፡፡

መንግሥት በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ትናንት ኚምሜቱ 5፡40 ላይ ማሹፋቾውን ዹገለጾ ሲሆን፣ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ስለ ሕመማቾውና አማሟታ቞ው ዝርዝር መግለጫ ኚመስጠት ተቆጥቧል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አመራር ዚወጡት ፖሊሲዎቜና ስትራ቎ጂዎቜ ተጠናክሹው እንደሚቀጥሉ ዹገለጾው መንግሥት፣ ዚአቶ ኃይለ ማርያምን ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትርነት አሹጋግጧል፡፡

ኚዛሬ ጀምሮ ዚቀብር ሥነ ሥርዓቱ እስኪፈጞም ድሚስ ብሔራዊ ዹሐዘን ቀን ታውጇል፡፡ ዚአገሪቱ ሰንደቅ ዓላማም ዝቅ ብሎ እንደሚውለበለብ አቶ በሚኚት አስታውቀዋል፡፡
http://www.ethiopianreporter.com 

Wednesday, August 15, 2012

Teddy Afro’s concert is scheduled to rock Addis Abeba for New Year eve


The highly anticipated Tewodros Kassahun a.k.a. Teddy Afro’s concert is scheduled to rock the capital on Ethiopian New Year eve at the Ghion Hotel. With his recent album release ‘Tikur sew’, Teddy Afro gained critical acclamation from his fans while setting the record for album sales by an Ethiopian artist in its first week of release.

Teddy Afro’s concert to blast AddisThis concert will be his second since his recent album release. With ticket sales already commenced since August 20, some 15,000 people are expected to attend the concert. The organizers say that they are expecting tickets be sold out well before the event.

The concert is expected to be transmitted live for a few minutes on Ethiopian Broadcasting Services (EBS), provided that they managed to reach an agreement. After the album release, Teddy had a concert on August 4 as part of the London the London Olympic Games. And he is yet to be back in Addis Ababa for the next concert. The concert seems be a highly anticipated event among his fans since it will be his first show after his latest release. The fans want to know how some of his popular new songs would sound on the stage. The closest he got to perform a song out his latest album is the new video clip ‘Tikur sew’ which was appreciated by his audience.


With four albums, Teddy Afro was able to climb to prominence in the local music scene. Teddy Afro is one singer, who is adored by many fans for the deep lyrics and courageous issues that he raised. Many people believe that within a short period of time, he is able to imprint his mark on Ethiopian music industry.

Source: EthiopianReporter

Tuesday, August 14, 2012

Ethiopian Maid kills her baby as she feared UAE consensual sex outside of marriage, court hears

The Nationals

DUBAI

A maid accused of murdering her baby hid its corpse in a suitcase because she was so scared of being punished for having sex outside of marriage, a court heard yesterday.

Prosecutors said that JA, a 29-year-old from Ethiopia, fell pregnant by AK, a 35-year-old Indian driver, in a consensual affair when he was working at her sponsor's house in Al Mutaineh 2 in August last year. She managed to keep the pregnancy secret from her employer throughout her term and gave birth unassisted in her room on April 24, 2012, using a knife to cut the umbilical cord. She claims the baby was born dead, but an autopsy showed the baby was born alive and was breast fed at least once before being dying of suffocation

Some while after the birth the maid's employers, an elderly Emirati couple, grew suspicious at the number of breaks she would request. The maid would use these to visit her room claiming she was tired.

The couple decided to book her a plane ticket home and asked their grandson AM, 17, to help. They kept the booking a secret but told the maid to shower and get dressed so they could all go out.

While she was in the shower they began to search her bags to see if she was hiding something. However, the maid noticed and rushed back out of the bathroom and tried to stop them.

The grandmother AH said she managed to check one of the maid's bags, but that when she tried to check a second one the maid rushed towards her and stopped her. The maid then grabbed an item wrapped in a black shayla and tried to flee the house. The family chased and caught the maid and found that the shayla contained the baby's dead body. They then called the police and reported the incident.

SS, a 22-year-old Emirati policeman, said that the baby's body showed signs of decomposition as the abdomen and face had turned green and swollen. "When I asked her why would she put the baby in a bag, she said she was scared she would be caught for having an illicit relation and an illicit child."

The maid and the driver are both on trial in the Misdemeanour Court charged with consensual sex outside of marriage - the maid will face a separate trial in the Criminal Court on the charge of premeditated murder.

Neither was present in the Misdemeanour Court yesterday, so the case was adjourned to September 9 to summon them.

Thursday, July 19, 2012

Ethiopia PM Meles in 'critical' state in Brussels



AFP – 21 hrs ago
Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi, a key player in the fight against Islamist extremists, was "critical" in hospital in Brussels Wednesday, diplomatic sources told AFP, though his government denied he was unwell.

The one-time Marxist who toppled the bloody dictatorship of Mengistu Haile Mariam in 1991 was in a life-threatening condition, said a diplomat who asked not to be named.

"He is in a critical state, his life is in danger," said the diplomat.

"He is in a critical state but is alive," said another.

In Addis Ababa, however, government spokesman Bereket Simon denied reports that the 57-year-old premier who has held power in the populous African nation for over two decades was ill. "He is not in a critical state. He is in good condition," the spokesman told AFP.

In Brussels, the Ethiopian embassy refused comment.

It said earlier this week that reports Meles was being treated at a hospital were "false and wrong", a rumour created by "an interest group which has preoccupied itself in disseminating such untrue stories".

But several diplomats in Brussels said he had been undergoing regular treatment on a private basis at one of the city's major hospitals for some time, and had been in hospital for some days.

No information was available on his illness and hospital officials declined comment on grounds of medical confidentiality.

His death could have dire consequences in the already unstable Horn of Africa, said diplomats in Brussels. "He has imposed his will on his neighbours" and is "a pole stability between Sudan, Eritrea and Somalia."

Questions surfaced about Meles's health when he missed a two-day African Union summit Sunday and Monday in Addis Ababa, apparently for the first time.

Meles's wife, herself a lawmaker, declined to talk to reporters about her husband.

One of the last times Meles was seen in public was at the G20 meeting in Mexico on June 19.

Dozens of African heads of state visited Ethiopia for the summit, including newly elected Egyptian President Mohamed Morsi, the first to do so since an assassination attempt in Ethiopia on former president Hosni Mubarak in 1995.

Benin's president and current AU chairman Thomas Boni Yayi said at the opening of the summit that the "unusual absence... cannot go unnoticed, because we know that Mr Meles is full of dynamism and leadership in our meetings".

Meles has been vilified by some as a dictator and praised by others as a visionary.

A key ally of the US in the fight against regional Al-Qaeda linked Islamists, Meles sent troops into Somalia to topple the Islamic Courts Union in 2006.

He sent troops back in five years later in 2011 to fight the Islamist group that had sprung up to replace the ICU, the Shebab.

Last week, UN human rights chief Navi Pillay condemned a "climate of intimidation" in Ethiopia after a court jailed a journalist for 18 years for "terrorism" and 23 other reporters and activists for between eight years and life.

Pillay said the overly broad definitions in a July 2009 anti-terrorism law had resulted in "criminalising the exercise of fundamental human rights".

Born May 8, 1955, Meles abandoned his medical studies before turning 20 to join the Tigray People's Liberation Front and fight Mengistu's regime.

In 1989, he took over the group's leadership and then forged a broader coalition with other regional movements to make up the Ethiopian People's Revolutionary Democratic Front (EPRDF), now the country's ruling party.

With US backing, the rebellion toppled Mengistu in 1991, a year after Meles abandoned Marxism.

Meles also fought a bitter war from 1998 to 2000 with neighbour Eritrea, which broke away from Ethiopia and won independence in 1993 after a 30-year struggle.

Twitter Delicious Facebook Digg Stumbleupon Favorites More