Check out changes at Finote Selam

Check out the new Finote Selam after being A capital city of W/Gojjam zone early this year.

Finote Selam new Music

new music by solomon demle .

public library in Finote Selam

time to support our people.

Finote Selam

time to support our people.

Thanks for Visiting

Saturday, May 26, 2012

ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ታስሮ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ትዕዛዝ ተላለፈ

አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በ1996 ዓ.ም. የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 436(ሐ)ን በመተላለፍ ፈጽሟል የተባለውን በሕገወጥ መንገድ መብትን የማስከበር ወንጀል፣ ለግንቦት 10 ቀን 2004 ዓ.ም. ቀርቦ እንዲያስረዳ በተላለፈለት ጥሪ መሠረት ባለመቅረቡ ታስሮ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ትዕዛዝ ተላለፈ፡፡ ትዕዛዙን ያስተላለፈው የፌዴራል መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የየካ ምድብ ወንጀል ችሎት ሲሆን፣ ኃይሌ ታስሮ እንዲቀርብ ትዕዛዝ ያስተላለፈው የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ሚያዝያ 18 ቀን 2004 ዓ.ም. ላቀረበው የወንጀል ክስ ግንቦት 10 ቀን 2004 ዓ.ም. መልስ ይዞ  እንዲቀርብ በተላለፈለት ጥሪ መሠረት ፍርድ ቤት ሳይቀርብ በመቅረቱ ነው፡፡


አትሌት ኃይሌን ለክስ ያበቃው ክስተት ህዳር 24 ቀን 2004 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡00 ሰዓት አካባቢ በየካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11/12 ክልል ልዩ ቦታው ሃያ ሁለት እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ በተፈጸመ ድርጊት ነው፡፡

በተጠቀሰው አካባቢ በሚገኘው የአትሌት ኃይሌ ሕንፃ ውስጥ ተከራይተው ከሚሠሩትና ተበዳይ ከሆኑት አቶ አዲስ ደገፋ ጋር በኪራይ ውል ምክንያት በተፈጠረ አለመግባባት ጉዳዩ ፍርድ ቤት ደርሶ በክርክር ላይ እንደነበር ክሱ ያስረዳል፡፡ ጉዳዩ በፍርድ ቤት ውሳኔ ሳያገኝ አቶ አዲስ ይሠሩበት የነበረውን ቢሮ ቁልፍ በሌላ ቁልፍ በመቀየር እንዳይገለገሉበት ማድረጉን ክሱ ያብራራል፡፡ ድርጊቱም በሕገወጥ መንገድ መብትን ማስከበር ወንጀል መሆኑን ጠቅሷል፡፡

አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ የፍርድ ቤቱን ጥሪ አክብሮ ፍርድ ቤት ባለመገኘቱ በ48 ሰዓታት ውስጥ ታስሮ ለግንቦት 29 ቀን 2004 ዓ.ም. ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡

Saturday, May 19, 2012

New Documentary yehune Belay About Felge Selam kidus Georgis Deber Bethe Christian


Sunday, May 6, 2012

Jacky Gosee Yene Akal New song


Twitter Delicious Facebook Digg Stumbleupon Favorites More