
የተማርንበትም የተማረርንበትም ሰሞን
(ፎቶው የቢቢሲ ነው)
click here for pdf
የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት ከተረዳበት ሰዓት ጀምሮ ሀገራችን አዲስ መልክ
ይዛለች፡፡ ያለፉት ቀናት ስለራሳችን የተማርንባቸው፤ በራሳችንም የተማረርንባቸው ቀናት ነበሩ፡፡ እስኪ ከተማርንባቸው ልጀምር፡፡
ትዝ ይለኛል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ከውጭ ሀገር ወደ አዲስ አበባ የሚገቡበት ጊዜ
ነበር፡፡ በቦሌ ጎዳና ፖሊሶች አዚህም እዚያም በዛ ብለዋል፡፡ እኔ ደግሞ አልሰማሁም ነበርና እዚያ አካባቢ ለሥራ መሄድ፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ መንገዱ ጭር አለ፡፡ ፖሊሶችም መጡና ከአካባቢው ዘወር እንድንል ነገሩን፡፡ የሚገርመው ነገር ግን አካባቢው
በአፓርታማዎች የተጠቀጠቀ ነበርና ዘወር የምንልበት ቦታ ጠፋን፡፡ ፖሊሱ ግን አሁንም አሁንም ከአካባቢው ዘወር እንል ዘንድ
ያዝዛል፡፡ ግን የት ዘወር እንበል? በመጨረሻ መጣና በአፓርታማው የታችኛው ክፍል ካሉት ቤቶች አንዱን አንኳኳ፡፡ አንዲት
በእድሜ ጠና ያሉ ሴት ከፈቱ፡፡ ‹‹ግቡ›› አለን ፖሊሱ፡፡ አንድ ሰባት እንሆናለን፡፡ ግራ ገብቶን ተያየን፡፡ ከጀርባችን...