Check out changes at Finote Selam

Check out the new Finote Selam after being A capital city of W/Gojjam zone early this year.

Finote Selam new Music

new music by solomon demle .

public library in Finote Selam

time to support our people.

Finote Selam

time to support our people.

Thanks for Visiting

Sunday, September 23, 2012

Teddy Afro New Wedding Song - Yemushiraye Enat


Tuesday, September 4, 2012

የተማርንበትም የተማረርንበትም ሰሞን



(ፎቶው የቢቢሲ ነው)
የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት ከተረዳበት ሰዓት ጀምሮ ሀገራችን አዲስ መልክ ይዛለች፡፡ ያለፉት ቀናት ስለራሳችን የተማርንባቸው፤ በራሳችንም የተማረርንባቸው ቀናት ነበሩ፡፡ እስኪ ከተማርንባቸው ልጀምር፡፡
ትዝ ይለኛል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ከውጭ ሀገር ወደ አዲስ አበባ የሚገቡበት ጊዜ ነበር፡፡ በቦሌ ጎዳና ፖሊሶች አዚህም እዚያም በዛ ብለዋል፡፡ እኔ ደግሞ አልሰማሁም ነበርና እዚያ አካባቢ ለሥራ መሄድ፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ መንገዱ ጭር አለ፡፡ ፖሊሶችም መጡና ከአካባቢው ዘወር እንድንል ነገሩን፡፡ የሚገርመው ነገር ግን አካባቢው በአፓርታማዎች የተጠቀጠቀ ነበርና ዘወር የምንልበት ቦታ ጠፋን፡፡ ፖሊሱ ግን አሁንም አሁንም ከአካባቢው ዘወር እንል ዘንድ ያዝዛል፡፡ ግን የት ዘወር እንበል? በመጨረሻ መጣና በአፓርታማው የታችኛው ክፍል ካሉት ቤቶች አንዱን አንኳኳ፡፡ አንዲት በእድሜ ጠና ያሉ ሴት ከፈቱ፡፡ ‹‹ግቡ›› አለን ፖሊሱ፡፡ አንድ ሰባት እንሆናለን፡፡ ግራ ገብቶን ተያየን፡፡ ከጀርባችን ገፋ ገፋ እያደረገ ሰው ቤት ውስጥ አስገባን፡፡ ስለ ቻይና ባቡርና ፖሊስ ያየሁት ፊልም ነው ትዝ ያለኝ፡፡ ሴትዮዋ በሩን እንዲዘጉ ተነገራቸው፡፡ ተዘጋ፡፡
አሁንም ሰው ቤት ገብተን ተያየን፡፡ ደግነቱ ሴትዮዋ ተግባቢ ናቸውና ‹‹በሉ እንግዲህ መንግሥት ካዛመደን ዐረፍ በሉና ሻሂ ጠጡ›› አሉን፡፡ እኛም ሳቅ እያልን ባገኘነው ወንበር ተቀመጥን፡፡ እዚያ ተቀምጠንም በባለ ሥልጣኖቻችንና በሕዝባቸው መካከል ስላለው ግንኙነት ተቸን፤ አማን፤ ሃሳብም ሰነዘርን፡፡ ከዚህ በፊት ያጋጠመንንም ተጨዋወትን፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስከሬን በመጣበት ማታ ይህንን አጋጣሚ ነበር የማስበው፡፡ ሕዝቡ ግልብጥ ብሎ መንገድ ላይ ወጥቶ ነበር፡፡ በአንዳንድ አደረጃጀቶች በኩል ከመጡ ጥቂት ሰዎች በቀር አብዛኛው ሰው በራሱ ፈቃድ ኀዘኑን ለመግለጥ ታሪክም ለማየት ነበር የወጣው፡፡ ጧፍ እንኳን ያበራው ዕለቱ የፍልሰታ ጾም ማብቂያ የኪዳነ ምሕረት ዋዜማ በመሆኑ በቦሌ መድኃኔዓለም፤ በኡራኤል፣ በእስጢፋኖስና በግቢ ገብርኤል አካባቢ ለበዓሉ ጧፍ ለመሸጥ ከተቀመጡት እናቶች እየገዛ ነበር፡፡ ጧፍ ማብራትን ሕዝቡ ራሱ ያመጣው የአቀባበል ሥርዓት ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ግን በየ ቀበሌው ተዳረሰ፡፡
ያን ምሽት ሕዝቡ ወደ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላምና ያለ አንዳች ችግር ሲገባ ነበር፡፡ ከፖሊስ ጋር ግርግር የፈጠረ አልነበረም፡፡ ጨዋነት ጎልታ የወጣችበት ምሽት ነበር፡፡ በመንገድም ላይ ቢሆን የነበረው ሁኔታ አስቀድሞ ያልተገመተው የሕዝቡ ማዕበል ከተጠበቀው በላይ መሆኑ ነበር፡፡ የጸጥታ አስከባሪዎች መጀመርያ ላይ አስከሬኑ ከሕዝብ ርቆ ግራና ቀኝም ተከልሎ እንዲያልፍ አስበው ነበር፡፡ ሕዝቡ ግን ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ እያለቀሰና እየተከዘ አብሮ መጓዝን መረጠ፡፡ ነገሩንም ሲረዱት እነርሱም ተውት፡፡ እንዲያ ዝናብ እየቀጠቀጠው፤ እንዲያ ብርድ እያንቀጠቀጠው የዐሥር ደቂቃ መንገድ አራት ሰዓት እስኪፈጅ ድረስ አስከሬኑን በክብር አጅቦ፤ ራሱ ባወጣው ሥርዓትና አሠራር ተጓዘ፡፡ ምንም ዓይነት የጸጥታ ችግር ሳይፈጠር አስከሬኑ ቤተ መንግሥት ደረሰ፡፡
ለመሆኑ ከዚህ መማር የለብንም?
የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨዋ ሕዝብ ነው ስንል ምን ማለታችን ነው?
ይህ ሕዝብ መሪዎች ወይም ባለ ሥልጣናት ባለፉ ባገደሙ ቁጥር ሊንገላታ የማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ሊከበር እንጂ ሊሰጋ የማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ቀርበው ሊያወያዩት፤ ችግሩን በቅርብ ሊያዩለት የሚገባ ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ወደ ሀገሪቱ ከሚመጡ እንግዶች በላይ ሊከበር የሚገባው ሕዝብ ነው ማለታችን ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝቶ ዘመዱን ለመቀበል አትገባም ውጭ ቆመህ ዝናብ ይቀጥቅጥህ ሊባል የማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ፍትሕ ለማግኘት ዓመት ሁለት ዓመት ሊጉላላ የማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ በጎ ለሚሠሩ ሁሉ ስሕተታቸውንና ጥፋታቸውን እያወቀ እንኳን የሚደግፍ ነውና ሊያሳዝኑትና ሊያቀስቀይሙት የማይገባ ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ኮንደሚንየም ብርቅ ሊሆንበት የመይገባ ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ለመጀመርያ ጊዜ በሕዝብ ታጅበው ቤተ መንግሥት ሲገቡ አየሁ፡፡ ምናለ በሕይወት በነበሩ ጊዜ ይህ ሆኖ በነበረ፡፡ ይኼው ሕዝብ ነውኮ ያኔም የነበረው፤ ይኼው ጨዋ ሕዝብ እኮ ነው የሚያጅባቸው፤ ይኼው ጨዋ ሕዝብ እኮ ነው የሚጠይቃቸው፤ የሚያወያያቸው፡፡ ይህ ሕዝብኮ እዚሁ የነበረ ነው፡፡ ከአውሮፓ ወይም ከእስያ አልመጣም፡፡ ቀጣዮቹም ባለሥልጣናት ይህንን ትምህርት መውሰድ አለባቸው፡፡ ባለ ሥልጣናት ሆይ ሰው ሁኑ፡፡ ሰው ያልሆነው አምላክ እንኳን ሰው ሆኖ በሰው ቋንቋ ተነጋግሯል፡፡ ከሰው ጋር ውሎ አድሯል፤ ከሰው ጋር በልቷል፡፡ ከሰው ጋር ተጉዟል፡፡ እናንተ ታድያ ሰው ብትሆኑና ከሰው ጋር ብትኖሩ ምናለበት? እርሱ አምላካችን ሰው ሆኖ የሰውን መከራ፣ ስቃይና ኀዘን ቀምሶታል፡፡ እናንተስ ሰው ሆናችሁ መከራችንን፣ ችግራችንንና ኀዘናችንን ብትቀምሱት ምናለ? እስከ መቼ በሪፖርትና በስብሰባ ብቻ እንገናኛለን? እስከ መቼ በቴሌቭዥን ብቻ እንተያያለን?
ሪፖርት ቢጽፉት እንደ አካል አይሆንም
ቴሌቭዥን ቢያዩት እንደ አካል አይሆንም
ስብሰባ ቢጠሩት እንደ አካል አይሆንም
እንገናኝና ልናገር ሁሉንም
ተብሎ መዘፈኑን አልሰማችሁም?
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ቤተ መንግሥት ተከፈተ፡፡ ይህ ደግሞ አቶ መለስ የሠሩት ሌላው ታሪክ ነው፡፡ እኔ ስለዚህ ቤተ መንግሥት ክፉ እንጂ ደግ ሰምቼ አላውቅም ነበር፡፡ በተለይ በደርግ ዘመን ስለነበረው ሁኔታ የተጻፉት ሁሉ ስለዚያ ቤተ መንግሥት የሆረር ፊልም ያህል ሲያስፈራሩን ነበር፡፡ ምናልባት ሕዝብ በብዛት ሆኖ ወደዚያ ቤተ መንግሥት የገባው በንጉሡ ጊዜ ግብር ለመብላት ሳይሆን አይቀርም፡፡ እርሱንም ሰምተን እንጂ አላየንም፡፡ ከዚያ ወዲያ ባለፉት ዓርባ ዓመታት ለሕዝብ የተከለከለ ቦታ ነበር፡፡ እንዴው አልፎ አልፎ ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት ካልኖረ በቀር ቤተ መንግሥቱና ሕዝቡ በማኅበራዊ ነገር አልተገናኝተውም ነበር፡፡
(ፎቶው የቢቢሲ ነው)
እነሆ ሕዝብ ተሰለፈና ቤተ መንግሥት ገባ፡፡ ይህንንም ቢሆን ሕዝብ የፈጠረው ይመስለኛል፡፡ የአቶ መለስ ሞት ከተረዳበት ሰዓት ጀምሮ ሚዲያዎቹን ያጨናነቀው ጥያቄ የት ሄደን ልቅሶ እንድረስ? የሚለው ነበር፡፡ የቀብር አስፈጻሚው ብሔራዊ ኮሚቴም ለዚህ በጎ ምላሽ በመስጠቱ ይመሰገናል፡፡ ወደ ቤተ መንግሥት እንደሚገባ በቀበሌም በአደረጃጀትም፣ በሚዲያም ከመነገሩ በፊት ነበር ሕዝብ ቤተ መንግሥቱን ያጥለቀለቀው፡፡ [እዚህም ላይ ሌላ አስመራሪ ነገር ገጥሞን ነበር፡፡ በሀገር ውስጥ ያሉት የመንግሥት ሚዲያዎች ሰው ግልብጥ ብሎ የወጣው የጠቅላይ ሚኒስትሩን ፖሊሲና ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ በመቀበሉና በመጠቀሙ ነው ይሉ ነበር፡፡ የውጮቹ ደግሞ ተገድዶና ተደልሎ ነው፤ አደርባይ ስለሆነም ነው ይላሉ፡፡ የሁለቱም ችግር ሕዝብን ካለ ማወቅና ለራሱ ጥቅም ሁሉንም ነገር ከመጎተት የመጣ ነው፡፡
አስከሬኑ አዲስ አበባ ሲገባም ሆነ በቤተ መንግሥቱና በየአካባቢው በተከናወነው ልቅሶ ሕዝቡ በፖሊሲዎችና በስትራቴጂዎች ሙሉ በሙሉ ተስማምቶ ብቻ የወጣ አይደለም፡፡ ምክንያቱ ልዩ ልዩ ነው፡፡ በርዕዮተ ዓለማቸውና በሥራቸው ተደስቶ ነገር ግን በሆነው ነገር አዝኖ የወጣ አለ፡፡ በአንዳንድ ሃሳባቸው ተስማምቶ በሌላው ተለያይቶ በመሞታቸው ግን አዝኖ የወጣ አለ፡፡ በእርሳቸው አስተሳሰብም ሆነ ሥራ ምንም ሳይስማማ፣ ነገር ግን የሀገሩ መሪ በመሞታቸው አዝኖ የወጣም አለ፡፡ ታሪክ ለማየት ሲልም የወጣም አለ፡፡ እርሳቸውን እየተቃወመም በባሕሉ ልቅሶ መድረስ አለብኝ ብሎ የወጣም አለ፡፡ ይህ ሁሉ እኛን ይደግፋል ብሎ ማሰብና በዚህ ተመሥርቶ ውሳኔ መወሰን ከስሕተት ይጥላል፡፡
ይህ ሕዝብ ተገድዶ የወጣ አድር ባይ ነው ብሎ ማሰብም ሌላው ስሕተት ነው፡፡ ምናልባት እንዲያውም አብዛኛው ኀዘኑን በባህሉ መሠረት ለመግለጥ የወጣ ነው፡፡ ጥቂት ሊገደዱ የሚችሉ ይኖራሉ፤ ታይተዋልም፡፡ ውጡ ብለው መመርያ ለማውጣት የሞከሩ ታናናሽ ባለ ሥልጣናትም ነበሩ፡፡ ሕዝቡ ግን የተጓዘው በራሱ ነው፡፡ መቼም ሕዝብን በግድ ማሰለፍና አደባባይ ማውጣት ይቻል ይሆናል እንጂ እንዲያለቅስ፣ እንዲደነግጥ፣ ፌንት እንዲያደርግ፤ መሬት እንዲንከባለል ማድረግ የሚቻል አይመስለኝም፡፡ በርግጥ ለደረት ድቂያ፣ ለአስለቀሽና ለእድር ድንኳን አንዳንድ ቅመማ ቅመም ሳይጨመርበት አይቀርም፡፡ ሁሉንም በአንድ ፋይል ጠቅልሎ ተታልሎ ነው፣ ተገድዶ ነው፣ አድር ባይ ሆኖ ነው ማለት ግን የኢትዮጵያን ሕዝብ አለመረዳትን የሚያሳብቅና ወደ ተሳሳተ ውሳኔም የሚያደርስ ነው፡፡]
ሕዝቡ ባህላዊ ሕዝብ ነው፡፡ አዛኝ ሕዝብም ነው፡፡ ያዘነበት የየራሱ ምክንያት አለው፡፡ አንድ ያደረገው ማዘኑ ነው፡፡ ራሳቸውን የሚስቱ፤ የሚያደርጉትን የማያውቁ፤ እየሆነ ያለውን ነገር መቀበል ያቃታቸው፤ የነገሮች መገጣ ጠም ያስደነገጣቸው፤ መሪ ሲሞት፤ ሲለቀስለትም አይተው ባለማወቃቸው ግራ የገባቸው ሰዎች ነበሩ፡፡ ሁሉም ግን አዝነው ነበር፡፡ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ ዐዋቂዎች፣ አረጋውያን፤ የተማሩ፣ የከተማ የገጠር ሁሉም ወደ አራት ሰዓታት የፈጀ ሰልፍ ይዘው ኀዘናቸውን ለመግለጥ ገብተዋል፡፡[እዚህ ላይ ግን ሌላ የሚያስመርር ነገር ነበር፡፡ ሕዝብ አዝኗል፡፡ ኀዘኑን የሚገልጥበት ቦታም ይፈልጋል፡፡ በባሕላችን ኀዘናችንን የምንገልጥበት ቦታ እንፈልጋለን፤ እገሌ ሞተ ሲባል ልቅሶ የሚደረሰው የት ነው? መባሉ የተለመደ ነው፡፡ አንዳንድ እወደድ ባዮች ግን ልቅሶውንና ወደ ቤተ መንግሥት መሄዱን እንደ ግዴታ ለማድረግ ሞክረዋል፡፡ ለምን? ይህ ከማማረር በቀር ምን ፋይዳ ይሰጣል? ወይስ እኛ ያልሠራነው ሥራ እንደ ተሠራ አይቆጠርም? በመጨረሻዎቹ ሦስት ቀናት በተደረገው የስንብት መርሐ ግብር ጊዜ በየአካባቢው የታየው አስገዳጅ የመሰለ ቅስቀሳ የሕዝቡን ስሜት ወደ መረበሽ ተሻግሮ ነበር፡፡ ፈጽሞ መደገም የሌለበት አስመራሪ አሠራር አንዱ ይኼ ነው፡፡]
ምንም እንኳን የሕዝቡ ቁጥር ከተጠበቀው በላይ ቢሆንም፤ ምንም ያህል ያልታሰበ ቢሆን ሕዝቡን ለማስተናገድና ሕዝቡም እንዳይቸገር ለማድረግ የጸጥታ አስከባሪዎች ያደርጉት የነበረው ጥረት ሊደነቅ ይገባዋል፡፡ የማመናጨቅ፤ የመሳደብ፤ የመገፍተር፣ አይቻልም አይቻልም ብሎ የመዝጋት ጠባይ አይታይም ነበር፡፡ መጀመርያ በአንድ በር ፤ በኋላም በሁለት በር፤ ከዚያም በዋናው በር በኩል በማስገባት በመስተንግዶ ሠልጥነዋል ከሚባሉት ከሆቴል አስተናጋጆች እንኳን በማይገኝ ትኅትናና ቅልጥፍና ለማስተናገድ ጥረዋል፡፡
እኔ ይህንንም ነገር ነው እንማርበትና እንቀጥል የምለው፡፡ ድሮ ድሮ ሌባና ፖሊስ ስንጫወት ፖሊስ አባራሪ ሌባ ተባራሪ ይሆን ነበር፡፡ ይህ ጨዋታ ሌባ በሌለበትም ሳይቀጥል አልቀረም፡፡ ሕዝብና ፖሊስ ተከባብሮ እንጂ ተፈራርቶ መኖር የለበትም፡፡ ፖሊስ ሕዝቡን የሚያገለግል፤ ለሕዝቡም ጸጥታ የሚተጋ መሆኑን ማስመስከር አለበት፡፡ ፖሊስን ወንጀለኛ ብቻ እንዲፈራው መደረግ አለበት፡፡ ‹‹ፖሊስ እጠራብሃለሁ›› እያሉ ልጆችን ማስፈራራት እንዲቀር ፖሊሶቹ ራሳቸው መሥራት አለባቸው፡፡
ይህ የአሁኑ ትውልድ ቤተ መንግሥት ምን እንደሚመስል፤ የሚመራው ሰው የት እንደሚሠራ፤ የት እንደሚኖር ለመጀመርያ ጊዜ ያየበት ዕድል ነው የገጠመው፡፡ እንዲያውም አንዳንዶች የጠቅላይ ሚኒስትሩን ቢሮና ቤት አይተው ተገርመዋል፡፡ እንደዚያ እንደማይመስላቸው ይናገሩ ነበር፡፡ ካሰቡት በታች ሆኖባቸው ‹‹እኒህ ሰው እዚህ ነበር እንዴ የሚኖሩት?›› ብለዋል፡፡ ለምን ግን የራሳችንን ቤተ መንግሥት በሕልም ብቻ እንድናየው ተደረገ? ለምንድን ነው ስለ መሪዎቻችን ብዙ ነገር እንዳናውቅ የሚደረገው? ብናውቅ ምን ይሆናል? ያኔስ ቢሆን አሁን ያወቅነውን አልነበር የምናውቀው? ምን የተለየ ነገር ነበረው?
ስለ አቶ መለስ ጠባያት፣ የሥራ ሁኔታ፤ ትጋትና ማንነት በሕይወታቸው እያሉ ከምናውቀው በላይ አሁን ነው የሰማነው፡፡ መስማታችን እሰየው፡፡ ግን ይህንን ቀደም ብሎ መስማት አይቻልም ነበር? በርግጥ እርሳቸው ስለ ራሳቸው መናገርም ሲነገር መስማትም ብዙም አይፈልጉም ነበር ይባላል፡፡ የርሳቸው አለመፈለግ መልካም፡፡ ግንኮ መሪ የሚፈልገውን ብቻ አይሠራም፤ ሕዝብ የሚያስፈልገውንም ጭምር እንጂ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ማለት ግለሰብነት ብቻ አይደለም፡፡ ሕዝባዊ አካልም ነው፡፡ ሕዝብ ስለ መሪው ማወቅ አለበት፡፡ ሊነገረው ይገባል፡፡ ስለ መሪው የማያውቅ ሕዝብ ሁለት ነገር ይገጥመዋል፡፡ ወይ ባለ ማወቅ መሪውን ይቃወመዋል፤ ወይም ባለ ማወቅ መሪውን ይደግፈዋል፡፡ ሁለቱም ግን አደገኞች ናቸው፡፡ ባለማወቅ የደገፈም ሲያውቅ ይሸሻል፤ ባለማወቅ የተቃወመም ሲያወቅ ይፀፀታል፡፡
ከሁሉም በላይ የተደነቅኩት ግን በቀብሩ ዕለት ነው፡፡ በሕይወቴ ይሆናል ብዬ ከማላስባቸው ነገሮች አንዱ የሆነውም ትናንት ነው፡፡ አንድ ወዳጄ ማታ ስደውልለት ‹‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቤት ጸሎተ ፍትሐት ልናደርግ መሄዳችን ነው›› አለኝ፤ አላመንኩትም፡፡ ሰዓቱ ከምሽቱ ወደ ሦስት ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡ ካህናቱ፣ ዲያቆናቱ፣ መሪጌቶቹ ተሟልተው ሙሉ ጸሎት ሲደረግ ነበር ያደረው፡፡ የቤተ መንግሥቱ ሰዎች ለጸሎቱ የነበራቸው ክብርና ሥነ ሥርዓት የሚገርም ነበር፡፡
ከዚያም የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የመጨረሻውን የጸሎት ሥነ ሥርዓት አሳየን [ግን ጋዜጠኞቹ ምን ነክቷቸው ነው? ሃይማኖታዊ ጸሎት ሲሉ የዋሉት፡፡ ለመሆኑ ሃይማኖታዊ ያልሆነ ጸሎት አለ? ‹ፍትሐት› የሚለው ቃል ጠፍቷቸው ነው? የቻይናው ቴሌቭዥን እንኳን ያወቀውን ቃል እነርሱ ምነው ጠፋቸው? ይባስ ብለው በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የነበረውን ጸሎት ‹ቅዳሴ› እያሉ ይጠሩት ነበር፡፡ ለነገሩማ ‹በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል› ለማለት ‹በቅድስት ካቴድራል ሥላሴ› ይሉ እንደነበር ስሰማ ይቅር ብያቸዋለሁ፡፡ ኧረ እንዲያውም የዛሬው ልቅሶ የሚያምር ልቅሶ ነው ያለን ጋዜጠኛም ነበር፡፡
 ሚዲያዎቻችን ከልምድ ማነስም ሊሆን ይችላ የችግርንና የኀዘንን ወቅት እንዴት መዘገብ እንደሚቻል መማር አለባቸው፡፡ ሁለት ሳምንት ሙሉ የፍቅር እስከ መቃብርን ዋሽንት ብቻ ከማሰማት የተለያዩ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት አይቻልም ነበር? ስለ አቶ መለስ ማንነት የሚያውቋቸውን ማነጋገር፤ የውይይት መርሐ ግብር ማዘጋጀት፤ ሌላም ሌላም አይቻልም ነበር? የቃለ መጠይቅ ጥያቅዎቹስ ለሕፃኑም፣ ለዐዋቂውም፣ ለተማረውም፣ ለማይሙም አንድዓይነት መሆን አለባቸው? ራሳቸው ጋዜጠኛ ራሳቸው ተንታኝ እንዲሆኑስ የቱ አሠራር ነው የፈቀደው? አንዳንዴ እንዲያውም  ስብከትም ሁሉ ይመስል ነበር? ደግሞስ ሰው አኳሽቶና አጋንኖ የሚናገረውን ነገር ሁሉ ማቅረብ አለባችሁ? ጋዜጠኞቻችንኮ ስለ አቶ መለስ ሁሉን ዐዋቂ ሆኑብን፤ ቢያንስ አብረዋቸው የተጓዙት፤ አብረዋቸው የሠሩት፤ አብረዋቸው የኖሩት፤ ስለ እርሳቸው የጻፉት ቀርበው ቢነግሩን ምናለ? ይቺ አሠራር ታስመርራለችና መታረም አለባት]፡፡
ወደ መስቀል አደባባይ የተጓዘውም ከፊትና ከኋላ ድባብ በያዙ ካህናት፣ ማዕጠንት በያዙም ጳጳሳት ታጅቦ ነበር፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝና ካለፈው ጊዜ ይልቅ የፓትርያርኩ ቀብር የመሰለን ይኼኛው ነው፡፡ የጉዞው ሥነ ሥርዓት አዘጋጆቹንም ሆነ አከናዋኞቹን ያስመሰገነ ነበር፡፡ እመለስበታለሁ፡፡
በመስቀል አደባባይ መርሐ ግብሩ በጸሎት መጀመሩን ሳይ ዓይኔ ነው ወይስ ቴሌቭዥኑ ነው? አሰኝቶኛል፡፡ ይህ እንዲሆን ያደረገ ማነው? የአቶ መለስ ኑዛዜ? የወይዘሮ አዜብ ፍላጎት? ወይስ የመንግሥት ፈቃድ? ከወሬ ባለፈ መረጃ ባውቀው እንዴት በወደድኩ፡፡ መቼም ሰው ሆኖ ከሥላሴ ቤት የሚቀር የለምና የአቶ መለስ አስከሬን ወደ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሲገባ የነበረውን ሥነ ሥርዓት ምነው ከሳምንት በፊት ልናየው አልቻልንም አሰኝቶኛል፡፡
አስከሬኑ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ቤተ መቅደሱን ዞሮ ነው ወደ መቃብሩ የገባው፡፡ ባለፈው ጊዜ ይህንን አላየሁምሳ? የካህናቱ ወረብ፣ የሰንበት ተማሪዎቹ መዝሙር፣ የአቡነ ናትናኤልና የአቡነ አረጋዊ ትምህርት ‹‹እውነት ለአቶ መለስ ነው ይህ የሚደረገው?›› አስብሎኛል፡፡ መለስ ከሕይወታቸው ይልቅ[በሕይወታቸው የሠሩትን እንዲህ በሚታይና በሚሰማ ደረጃ ስለማላውቅ] በሞታቸው ቤተ ክርስቲያንን ከፍ ከፍ አድርገዋታል፡፡
ይህቺ ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል ክብርና ሞገስ እንደምትሆን ተተኪዎችም ትምህርት ይወስዳሉ ብዬ አስባለሁ፡፡
መሪ በመፈንቅለ መንግሥት ሳይገለበጥ፤ በጦርነት ተሸንፎ አገር ጥሎ ሳይወጣ፤ በአብዮት ከዙፋን ወርዶ እሥር ቤት ሳይገባ በተፈጥሮ ሞቶ በክብር ሲቀበር ለእኔ ትውልድ አዲስ ታሪክ ነው፡፡ የኔ ትውልድ ስለ መሪው ስደትና ሞት ሲሰማ እንጂ መሪውን አልቅሶ ሲቀብር አላየሁም፡፡ መለስ በዚህ ታሪክ ሠርተዋል፡፡
ከቤተ መንግሥት እስከ መስቀል አደባባይ፤ ከመስቀል አደባባይ እስከ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የነበረው ሥነ ሥርዓት አዘጋጆቹንም፣ ተሳታፊዎቹንም የሚያስመሰግን ነበር፡፡ የፕሮግራሙ በተያዘለት ሰዓት ማለቅ፡፡ በተለይም አቶ ኩማ ደቅሳ እንኳንም መድረኩን ለ‹‹አርቲስቶች›› አልሰጡብን ብያቸዋለሁ፡፡ እንዲህ እጥር ምጥን አድርገው አይመሩልንም ነበር፡፡ [በዚሁ ግን አንድ አስመራ ነገር መናገር ያስፈልጋል፡፡ ሰሞኑን ይወጡ የነበሩ ግጥሞች ከታገል ሰይፉ ግጥም በቀር ሚዛን የሚደፋ አጣሁ፡፡ ትትትትትት፣ንንንንንን፣ ችችችችችች፣ ምምምምምም ብቻ የተደረደረባቸው ናቸው፡፡ አንባቢዎችም ለመድረኩ የማይመጥኑ፣ ግጥሙንም ወደ ስድ ንባብ በመቀየር የተካኑ ናቸው፡፡ ከተዘፈኑትም መካከል ከአንዱ በቀር የግጥም ለዛ ያለው የለም፡፡ ምነው ለቸበር ቻቻ እንጂ ለኀዘን የሚሆን ግጥም አጣንሳ]
ያ እንደ ደዶፍ የወረደው ዝናብ ሥነ ሥርዓቱን ሳያሰናክለው፡፡ ከፖሊሶቹና ከወታደሮቹ ቆብ ላይ ዝናቡ እንደ ጣራ ፍሳሽ እየወረደ ሥነ ሥርዓቱ ግን ቀጠለ፡፡ መንገዱ ሁሉ ጎርፍ ነበረ፡፡ ተጓዦቹ ግን ችግሩ ሳይፈታቸው እነርሱም ጨዋነታቸውን አሳይተዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያኑ የነበረው ሥነ ሥርዓትም በተያዘው ሰዓት የተከናወነና ለዓይን የማይጎረብጥ ነበር፡፡ አቶ መለስ ተነሥተው የሰሞኑን ሁኔታ ቢያዩ በአንዳንዱ ነገር የሚገረሙና የሚደነቁ፤ በአንዳንዱ ነገር የሚያዝኑና የሚቆጩ፣ በአንዳንዱም ነገራችን የሚናደዱ ይመስለኛል፡፡
በዚያም ተባለ በዚህ ግን አቶ መለስ በሞታቸው ታሪክ ሠሩ፤ እኛም በሳቸው ሞት ታሪክ አየን፡፡ 
Source Daniel Kibret's view 

Tuesday, August 21, 2012

Ethiopia - Information Minister, Bereket Simon Press conference on the death of Meles Zenawi


አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ Haile Mariam Desalegne named acting Prime Minister




የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሕልፈተ ሕይወት አስመልክቶ መግለጫ የሰጠው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በሙሉ ሥልጣን አገሪቱን እንደሚመሩ አስታወቀ፡፡

በሚኒስትር ማዕረግ የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ በረከት ስምኦን በሒልተን ሆቴል ዛሬ ማለዳ በሰጡት መግለጫ፣ አቶ ኃይለ ማርያም በተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትርነት አገሪቱን ይመራሉ ብለው፣ በሚቀጥለው መስከረም መጨረሻ የሚሰበሰበው ፓርላማ የሚቀጥለውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን የቀብር ሥነ ሥርዓት የሚያስፈጽም ሰባት አባላት ያሉት ብሔራዊ ምክር ቤት መቋቋሙንም አቶ በረከት አስረድተዋል፡፡

መንግሥት በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ትናንት ከምሽቱ 5፡40 ላይ ማረፋቸውን የገለጸ ሲሆን፣ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ስለ ሕመማቸውና አማሟታቸው ዝርዝር መግለጫ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አመራር የወጡት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የገለጸው መንግሥት፣ የአቶ ኃይለ ማርያምን ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትርነት አረጋግጧል፡፡

ከዛሬ ጀምሮ የቀብር ሥነ ሥርዓቱ እስኪፈጸም ድረስ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ታውጇል፡፡ የአገሪቱ ሰንደቅ ዓላማም ዝቅ ብሎ እንደሚውለበለብ አቶ በረከት አስታውቀዋል፡፡
http://www.ethiopianreporter.com 

Wednesday, August 15, 2012

Teddy Afro’s concert is scheduled to rock Addis Abeba for New Year eve


The highly anticipated Tewodros Kassahun a.k.a. Teddy Afro’s concert is scheduled to rock the capital on Ethiopian New Year eve at the Ghion Hotel. With his recent album release ‘Tikur sew’, Teddy Afro gained critical acclamation from his fans while setting the record for album sales by an Ethiopian artist in its first week of release.

Teddy Afro’s concert to blast AddisThis concert will be his second since his recent album release. With ticket sales already commenced since August 20, some 15,000 people are expected to attend the concert. The organizers say that they are expecting tickets be sold out well before the event.

The concert is expected to be transmitted live for a few minutes on Ethiopian Broadcasting Services (EBS), provided that they managed to reach an agreement. After the album release, Teddy had a concert on August 4 as part of the London the London Olympic Games. And he is yet to be back in Addis Ababa for the next concert. The concert seems be a highly anticipated event among his fans since it will be his first show after his latest release. The fans want to know how some of his popular new songs would sound on the stage. The closest he got to perform a song out his latest album is the new video clip ‘Tikur sew’ which was appreciated by his audience.


With four albums, Teddy Afro was able to climb to prominence in the local music scene. Teddy Afro is one singer, who is adored by many fans for the deep lyrics and courageous issues that he raised. Many people believe that within a short period of time, he is able to imprint his mark on Ethiopian music industry.

Source: EthiopianReporter

Tuesday, August 14, 2012

Ethiopian Maid kills her baby as she feared UAE consensual sex outside of marriage, court hears

The Nationals

DUBAI

A maid accused of murdering her baby hid its corpse in a suitcase because she was so scared of being punished for having sex outside of marriage, a court heard yesterday.

Prosecutors said that JA, a 29-year-old from Ethiopia, fell pregnant by AK, a 35-year-old Indian driver, in a consensual affair when he was working at her sponsor's house in Al Mutaineh 2 in August last year. She managed to keep the pregnancy secret from her employer throughout her term and gave birth unassisted in her room on April 24, 2012, using a knife to cut the umbilical cord. She claims the baby was born dead, but an autopsy showed the baby was born alive and was breast fed at least once before being dying of suffocation

Some while after the birth the maid's employers, an elderly Emirati couple, grew suspicious at the number of breaks she would request. The maid would use these to visit her room claiming she was tired.

The couple decided to book her a plane ticket home and asked their grandson AM, 17, to help. They kept the booking a secret but told the maid to shower and get dressed so they could all go out.

While she was in the shower they began to search her bags to see if she was hiding something. However, the maid noticed and rushed back out of the bathroom and tried to stop them.

The grandmother AH said she managed to check one of the maid's bags, but that when she tried to check a second one the maid rushed towards her and stopped her. The maid then grabbed an item wrapped in a black shayla and tried to flee the house. The family chased and caught the maid and found that the shayla contained the baby's dead body. They then called the police and reported the incident.

SS, a 22-year-old Emirati policeman, said that the baby's body showed signs of decomposition as the abdomen and face had turned green and swollen. "When I asked her why would she put the baby in a bag, she said she was scared she would be caught for having an illicit relation and an illicit child."

The maid and the driver are both on trial in the Misdemeanour Court charged with consensual sex outside of marriage - the maid will face a separate trial in the Criminal Court on the charge of premeditated murder.

Neither was present in the Misdemeanour Court yesterday, so the case was adjourned to September 9 to summon them.

Thursday, July 19, 2012

Ethiopia PM Meles in 'critical' state in Brussels



AFP – 21 hrs ago
Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi, a key player in the fight against Islamist extremists, was "critical" in hospital in Brussels Wednesday, diplomatic sources told AFP, though his government denied he was unwell.

The one-time Marxist who toppled the bloody dictatorship of Mengistu Haile Mariam in 1991 was in a life-threatening condition, said a diplomat who asked not to be named.

"He is in a critical state, his life is in danger," said the diplomat.

"He is in a critical state but is alive," said another.

In Addis Ababa, however, government spokesman Bereket Simon denied reports that the 57-year-old premier who has held power in the populous African nation for over two decades was ill. "He is not in a critical state. He is in good condition," the spokesman told AFP.

In Brussels, the Ethiopian embassy refused comment.

It said earlier this week that reports Meles was being treated at a hospital were "false and wrong", a rumour created by "an interest group which has preoccupied itself in disseminating such untrue stories".

But several diplomats in Brussels said he had been undergoing regular treatment on a private basis at one of the city's major hospitals for some time, and had been in hospital for some days.

No information was available on his illness and hospital officials declined comment on grounds of medical confidentiality.

His death could have dire consequences in the already unstable Horn of Africa, said diplomats in Brussels. "He has imposed his will on his neighbours" and is "a pole stability between Sudan, Eritrea and Somalia."

Questions surfaced about Meles's health when he missed a two-day African Union summit Sunday and Monday in Addis Ababa, apparently for the first time.

Meles's wife, herself a lawmaker, declined to talk to reporters about her husband.

One of the last times Meles was seen in public was at the G20 meeting in Mexico on June 19.

Dozens of African heads of state visited Ethiopia for the summit, including newly elected Egyptian President Mohamed Morsi, the first to do so since an assassination attempt in Ethiopia on former president Hosni Mubarak in 1995.

Benin's president and current AU chairman Thomas Boni Yayi said at the opening of the summit that the "unusual absence... cannot go unnoticed, because we know that Mr Meles is full of dynamism and leadership in our meetings".

Meles has been vilified by some as a dictator and praised by others as a visionary.

A key ally of the US in the fight against regional Al-Qaeda linked Islamists, Meles sent troops into Somalia to topple the Islamic Courts Union in 2006.

He sent troops back in five years later in 2011 to fight the Islamist group that had sprung up to replace the ICU, the Shebab.

Last week, UN human rights chief Navi Pillay condemned a "climate of intimidation" in Ethiopia after a court jailed a journalist for 18 years for "terrorism" and 23 other reporters and activists for between eight years and life.

Pillay said the overly broad definitions in a July 2009 anti-terrorism law had resulted in "criminalising the exercise of fundamental human rights".

Born May 8, 1955, Meles abandoned his medical studies before turning 20 to join the Tigray People's Liberation Front and fight Mengistu's regime.

In 1989, he took over the group's leadership and then forged a broader coalition with other regional movements to make up the Ethiopian People's Revolutionary Democratic Front (EPRDF), now the country's ruling party.

With US backing, the rebellion toppled Mengistu in 1991, a year after Meles abandoned Marxism.

Meles also fought a bitter war from 1998 to 2000 with neighbour Eritrea, which broke away from Ethiopia and won independence in 1993 after a 30-year struggle.

Twitter Delicious Facebook Digg Stumbleupon Favorites More